የጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን
ራዕይ የክልሉ ፖሊስ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን የተከተለ የሰው ኃይሉም ብቃት በዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ የታነፀ ጊዜው የሚጠይቀውን ዘመናዊና የሰለጠነ ብቃት ያለው በድርጅት የተሟላ ሕዝባዊ የፖሊስ አገልግሎ መስጠት የሚችል ተቋም ተገንብቶ የወንጀል ሥጋቶች ቀንሰው ሕብረተሰቡ የመብቱ ተጠቃሚ ሲሆን ማየት፡፡ ተልዕኮ ሕገ-መንግሥቱንና ሌሎች ሕጎችን በማክበር የህዝቡን ተሳትፎ መሠረት በማድረግ ወንጀልንና የወንጀልን ሥጋትን በመከላከልና በመመርመር የህዝቡን ሠላምና ፀጥታ ማስፈን፡፡ እሴት * ለሀገሪቱ ሕገ-መንግስትና ለክልሉ ሕገ-መንግስት መከበር ዘብ እንቆማለን * ለሕብረተሰቡ ቅንና ታማኝ በመሆን አገልጋይነታችንን እናረጋግጣለን * መልካም ስነ-ምግባርን በመላበስ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን እንዋጋለን * ለሙያችንና ለዓርማችን ክብር እንሰጣለን * ምስጢር መጠበቅ መለያችን ነው * ፅናት መስዋዕትነት ሰብዓዊነት መለያችን ነው * ወንጀልን የሚጠላ ሕዝባዊ አመለካከት ያለው ፖሊስ እንሆናለን * ግልፀኝነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር እንከተላለን * ቆራጥ ትሁትና ደፋር ለፀረ-ሕዝብ ኃይል የማይበገር ፖሊስ እናደራጃለን * የቡድን አሠራርን መርህ እንከተላለን * ወንጀልንና የትራፊክ አደጋን በጋራ በመከላከል በሕዝብና በንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመቀነስ ተግተን እንሠራለን * ወንጀል የዕድገት ፀር ነው፡፡