Search results for - assosa

  • የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት

    Governmental Organizations

    የቤኒሻንጉል ጉምዝ ስራ አመራር ተቋም በአዋጅ ቁጥር 89/2002ዓ/ም ተቋቋመ፡፡ ተልዕኮ፤ በክልሉ ዉስጥ የሚገኙትን ተቋማት በሥራ አመራር መስክ ችግር ፈቺ የሆነ ጥናትና ምርምር በማድረግና በፍላጎት ላይ የተመሰረተ የሥልጠናና ምክር አገልገሎት በመስጠት የመፈፀምና የማስፈፀም አቅማቸዉን ማጎልበት፡፡ ራዕይ በ2012 ዓ.ም በሀገራችን የላቀ የሥራ አመራር ልማት ማዕከል ሆኖ ማየት፣ እነዚህን ራዕይ እና ተልዕኮ በተሟላ መልኩ ለማሳካት የምንሰጣቸው ዋናዋና አገልግሎቶች፤ ስልጠናዎችን መስጠት እና ማስተባበር፣በለውጥ ፕሮግራሞች እና በአዳዲስ አስራሮች ዙሪያ የምክር አገልግሎት መስጠት፣ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናትና ምርምሮችን ከማካሄድ ጎን ለጎን የመዝናኛ፣የመኝታ፣የካፍቴሪያ፣የቤተመጽሀፍት፣የኢንተርኔት፣የመማሪያክፍሎችእና የመሰብሰቢያ አዳራሽ አገልግሎቶች ሲሆኑ የሰው ሀብት በማልማት፣በጥናትና ምርምር ችግሮችን እየፈታን ለክልላችን እድገት የድርሻችንን ሀላፊነት ለመወጣት ለምናደርገው ጥረት መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት/ድርጅቶች/ የአብረን እንስራ መልዕክታችን ይድረሳችሁ፡፡

    091 183 9713
  • የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን

    ሠላም በብዙ መንገድ የሚተረጎም ቃል ነው፡፡ በስምምነትና በአንድነት አብሮ መኖር ነው፡፡ ደግሞም የዕረፍት ስሜት ነው፡፡ ሠላም ሰዎች ሲገናኙ የሚለዋወጡት የሠላምታ ቃል፣ወይም የንግግር መክፈቻ ቃል ነው፡፡ በመሆኑም ከአንድ ግለሰብ ጀምሮ እስከ ሀገር ብሎም ለዓለም መግባባትና አንድነት አስፈላጊ ነው፡፡ ሠላም፡፡ በተለይም ለዲሞክራሲ፣ ለልማትና ዕድገት መረጋገጥ ሠላም ወሳኝ ነው፡፡ እንደሚታወቀው ክልላችን ብሎም ሀገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የመጀመሪያውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በስኬት በማጠናቀቅ 2ኛውን ጀምራ ፈጣን ተከታታይ የኢኮኖሚ ዕድገት በማስመዝገብ ላይ ትገኛለች፡፡ ለቀጣይ የህዳሴ ጉዟችን መሠረት የሚሆኑ የበርካታ ታላላቅ ሜጋ ፕሮጀክቶች ተግባሪና ባለቤትም ሆናለች፡፡ ለተመዘገበው ፈጣንና ተከታታይ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት አስተማማኝ ሠላም በመፍጠር የክልላችን ፖሊስ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ በመጫወትም ላይ ይገኛል፡፡

    057 775 2875
  • ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን

    P.O.Box 74

    በክልላችን እየተመዘገበ ያለዉ የልማት ዕድገት ፈጣን፤ ቀልጣፋና ቀጣይነት እንድኖረዉ፤መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን፤ሰላም እንዲረጋገጥ በማድረግ የታራሚዎችን ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል የአምስት ዓመቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሸን ዕቅድ በማዘጋጀት በየዞን ማ/ቤቶች ባሉ የአደረጃጀትና የአመራር ክፍሎች ሰፊ ዉይይት ተደርጎበት የጋራ መግባባትን በመፍጠርና በየደረጃዉ ፈጻሚ ሀይል በማዘጋጀት ለተግባራዊነቱ ርብርብ በመድረጉ በማረም ማነጽ፤በአያያዝና ጥበቃ ዘርፎች የታራሚዎችን ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ የሚችሉ አበርታች ዉጤቶች ተመዝግቧል፡፡

    057 775 0137
  • የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት ገጠር መንገዶች ባለሥልጣን

    የተገነቡ መንገዶችን በመጠገንና በመንከባከብ የማያቋርጥ ምቹ አገልግሎት እንዲሠጡ ማድረግ፣

    057 775 0326
  • የኒንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት ንግድ፣ኢንዱስትሪና ትራንስፖርት ቢሮ

    P.O.Box 46
    Governmental Organizations

    1. ራዕይ፤ የንግድ፤ ኢንዱስትሪና ትራንስፖርት ዘርፎች ለምቶ፤ ተስፋፍቶ፤ ሕግና ሥርዓት ተከብሮ መብቱና ደህንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብ ተፈጥሮ ማየት፡፡ 2. ተልዕኮ፤ ጥራት ያለዉ የትራንስፖርት መሰረተ- ልማት በማስፋፋት፤ አስተማማኝና ደህንነቱ የተጠበቀ የጭነትና የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ተደራሽነት በማረጋጋጥ፤ ቀልጣፋ የግብይት ስርዓት በማስፈን ሕግና ሥርዓትን በማክበር፤ ፍትሃዊ የንግድ ዉድድር በማስፈን፤ የሸማቾች መብትን በማክበር የኢንዱስትሪ ልማት በማፋጠን የክልሉን ኅብረተሰብ ተጠቃሚነትና እርካታ ማረጋገጥና ተጠቃሚ ማድረግ ፡፡ 3. እሴቶች፤ * በመንግሥት የወጡ ሕጎች፤አዋጆች፤ ደንቦችና መመሪያዎችን በመጠበቅና በመከተል እንሠራለን፤ * ለደንበኞች እርካታ ቅድሚያ ትኩረት እንሰጣለን፣ * ግልጽነትና ተጠየቂነት ያለው አሰራርን እናሰፍናለን፣ * ዉጤታችንም ሆነ ዉድቀታችን የጋራችን ነዉ ' * uÖ”"^ ¾Y^ }’Xi’ƒ S”ðe Iw[}cu<” እናገለግላለን፣ * ለክልሉ ልማትና እድገት በቁርጠኝነት እንቆማለን፣ * ለደንበኞች ያለአድሎ በእኩልነት፣ በታማኝነት፤ በቅንነት፤ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት እንሰጣለን፣ * ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን በመከተ ለኪራይሰብሳቢነትን እንፀየፋለን፣ * በሥራው ውጤት ብቻ እንመዘናለን፣ * ሁልጊዜ ከተግባር እንማራለን፣ * ቅንጅታዊ ሥራችን መለያችን እናደርጋለን፤

    057 775 0124