የደቡብ ኦሞ ዞን አስተዳደር ፅህፈት ቤት
Arbaminch, Ethiopiaደቡብ ኦሞ ዞን በደቡብ በብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ ከሚገኙ 14 ዞኖች አንዷ ስትሆን ከነዚሁ አቻ ዞኖች በቆዳ ስፋቷ ቀዳሚ ናት፡፡በደቡብ ኬንያ፣በሰሜን ጋሞጎፋ ዞንና ኮንታ ልዩ ወረዳ፣በምዕራብ ደቡብ ሱዳንና ቤንች ማጂ፣በምስራቅ የሰገን አከባቢ ሕዝቦች ዞን የደ/ኦሞ ዞንን ያዋስናሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር በክልሉ ከሚገኙት 56 ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መካከል 16ቱ የሚገኙባት መሆኗንም ታዋቂ ያደርጋታል፡፡ የዞኑ ርዕሰ ከተማ የሆነችው ጂንካን ጨምሮ በአንድ ከተማ አሰተዳደር፣ በ2 አርሶ አደርና 6 አርብቶ አደር ወረዳዎቿ በ1999 ዓ.ም የህዝብና ቤቶች ቆጠራ መረጃ መሰረት በጠቅላላው 724,183 ህዝብ በመፈቃቀርና በመተሳሰብ የሚኖርባት ዞን ናት፡፡16ቱም ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ህገመንግስቱ ባጎናፀፋቸዉ መብት ተጠቅመው የየራሳቸው ቋንቋ፣ታሪክ፣ባህልና እምነት በመንከባከብና በማስፋፋት እየኖሩ ያሉ ዜጎች ከመሆናቸዉም ባሻገር ልዩነታቸው ለዞናዊ አንድነታቸው ዉበት ፈጥሮላቸዋል፡፡